” በእስልምና አስተምህሮ የአንድን ሰው ሕይወት ማዳን ዓለምን ማዳን ነው ” – ኡስታዝ አቡበከር አሕመድ….. Leave a comment

በአፋር እና በሶማሊ (ኢሳ) ወንድማማች ሕዝቦች መካከል የተኩስ አቁም ስምምነት መደረሱ ተነግሯል።

ይህ ስምምነት በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ፕሬዚደንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም አደራዳሪነት የተደረሰ መሆኑን ም/ቤቱ ገልጿል።

ከሁለቱ ክልሎች የተውጣጡ የሀገር ሽማግሌዎች ለበርካታ ወራት ሲያወያዩ ሰላምን ለመፍጠር ሲመክሩ እንደነበር ተነግሯል።

በመጨረሻም ፥ በአፋር እና በኢሳ ማኅበረሰቦች መካከል የነበረውን የወንድማማቾች ደም መፋሰስ እንዲቆም የሁለትዮሽ ስምምነት ላይ ተደርሶ የተኩስ አቁም ስምምነት ተደርጓል።

የጠቅላይ ም /ቤቱ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚደንት ሼይኽ አብዱልከሪም ሼይኽ በድረዲን ፤ ስምምነቱ ውጤታማ እንዲሁን የሁለቱም ክልል መንግስታት ትልቅ ኃላፊነት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤት የፕሬዚደንቱ ልዩ አማካሪ ዑስታዝ አቡበከር አሕመድ በሁለቱ ወንድማማች ሕዝቦች መካከል የነበረው ደም መፋሰስ ” በምሥራቅ አፍሪካ ረጅም ዘመን ያስቆጠረ ነው ” ብለዋል።

አሁን ላይ በተደረገው ጥረት ሰላም እንዲሰፍን የሚያስችል ውጤት መገኘቱ ገልጸዋል።

በእስልምና አስተምህሮ የአንድን ሰው ሕይወት ማዳን ዓለምን ሁሉ ማዳን መሆኑን ገልጸው ፥ ” በመነጋገር ችግሮችን የመፍታት አካሄድ የሰላም ችግር ባሉባቸው በሌሎችም የሀገራችን ክልሎች ሁሉ ሊተገበር ይገባል ” ብለዋል።

 

በድህረ ገጻችን ኢትዮ አማዞን በመግባት የሚፈልጉትን እቃ ማዘዝ  ብቻ  ሳይሆን የርስዎንም እቃዎች መሸጥ እንደሚችሉ ስናሳውቅዎት በደስታ ነው ። ለማስታወቂያ ወይንም ለመግቢያ ምንም ክፍያ አይጠበቅብዎትም፤  ለተጨማሪ መረጃ   ድህረ ገጻችንን ይጎብኙ። https://ethio-amazon.com/

ለበለጠ መረጃ ሊንኩን በመንካት የቴሌግራም ግሩፓችንን ይቀላቀሉ!https://t.me/ethioamazon

ምንጭ ፡-(@tikvahethiopia)

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Cart

Your Cart is Empty

Back To Shop

የሚፈልጉትን ይዘዙን

Order what you want