” ከ4 በላይ ወረርሽኞች ተከስተዋል። ከ2,400 በላይ ሰዎች በወረርሽኙ ተጠቅተዋል። ከፍተኛ ሞት አለ ” – የዋግኸምራ ብሔረሰብ ጤና መምሪያ…… Leave a comment

በአማራ ክልል ፤ በዋግኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ከተከሰተ በሰነበተው ድርቅ ሳቢያ ከአራት በላይ ወረርሽኞች መከሰታቸውን ተከትሎ ሰዎችና እንስሳት እየሞቱ መሆኑን ዞኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።

የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊው አቶ አሰፋ ነጋሽ በሰጡት ቃል፣ ” ከ4 በላይ ወረርሽኞች ተከስተዋል። ከ2,400 በላይ ሰዎች በወረርሽኙ ተጠቅተዋል። ከፍተኛ ሞት አለ ” ብለዋል።

በወረርሽኙ ምን ያህል ሰዎች ሞተዋል ? ለሚለው ጥያቄ፣ ” ሞቱ ከፍተኛ ነው። ቁጥሩን Specifically ለመናገር እርግጠኛ አይደለሁም ” ነው ያሉት።

ቢያንስ ከ5,000 በላይ እንስሳት እንደሞቱ፣ ለመከተብ አቅም እንዳልተገኘ፣ በሽታው (አባሰንጋ) ከእንስሳት ወደ ሰው እየተላለፈ መሆኑን ገልጸው፣ ከአንድ ወረዳ ብቻም ወደ  140 ሰዎች አባሰንጋ እንደተላለፈባቸው አስረድተዋል።

– ኮሌራ
– ኩፍኝ
– እከክና
– አባሰንጋ (የከብት በሽታ) እና ሌሎች ወረርሽኞች በሁሉም በሚባል ደረጃ በብሔረሰብ አስተዳደሩ ላይ ተከስተዋል ሲሉ ተናግረዋል።

” ኩፍኝ በሁሉም ወረዳዎች ተከስቷል። በጣም ብዙ ቁጥር ያላቸው ህፃናት ታመውብናል ” ያሉት አቶ አሰፋ፣ ” ለወረርሽኙ ምላሽ ክትባት እየሰራን ነው ” ብለዋል።

” እከክ በተለይ ድርቁ በስፋት ባጠቃቸው ወረዳዎች ተከስቶ ነበር ለመቆጣጠር እየተሞከረ ነው። የውሃ አቅርቦት፣ የንጽህ እና መጠበቂያ ግብዓት ካልቀረበ እሱንም መቅጣጠር እጅግ አስቸጋሪ ነው ” ነው ያሉት።

ድርቅ ከመከሰቱ በፊትም አካባቢው ትርፍ አምራች ስላልነበር የምግብ እጥረት እንደነበር አሁን የድርቁ መከሰት የምግብ እጥረቱን እጅጉን እንዳባባሰው ፤ የሥርዓተ ምግቡን ችግርም መቀልበስ እንዳልተቻለ አስረድተዋል።

ሞቱን ለመከላከል የሚሰጠውን ህክምና አጠናክረው እንደቀጠሉ የገለጹት ኃላፊው፣ ” በተለይ መካከለኛ የምግብ እጥረት ያለባቸውን ህጻናትና እናቶች ተደራሽ ለማድረግ የጸጥታ ችግሩ በጣም አስተቸጋሪ ሆኗል ” ብለዋል።

የዓለም ምግብ ፕሮግራም እርዳታዎች እንደተቀዛቀዙ አስረድተው፣ ” በጸጥታ ምክንያት ተደራሽ ያልሆኑ እናቶችና ህጻናት ምንም እየተደረገላቸው አይደለም ” ብለዋል።

ያለው የምግብ እጥረት በቋሚነት ካልተቀረፈ ችግሩን መቀልበስ ፈተና ስለሆነ አጋር ድርጅቶች ርብርብ ኦንዲያደርጉ ዞኑ ጥሪ አቅርቧል።

በድህረ ገጻችን ኢትዮ አማዞን በመግባት የሚፈልጉትን እቃ ማዘዝ  ብቻ  ሳይሆን የርስዎንም እቃዎች መሸጥ እንደሚችሉ ስናሳውቅዎት በደስታ ነው ። ለማስታወቂያ ወይንም ለመግቢያ ምንም ክፍያ አይጠበቅብዎትም፤  ለተጨማሪ መረጃ   ድህረ ገጻችንን ይጎብኙ። https://ethio-amazon.com/

ለበለጠ መረጃ ሊንኩን በመንካት የቴሌግራም ግሩፓችንን ይቀላቀሉ!https://t.me/ethioamazon

ምንጭ ( @tikvahethiopia)

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Cart

Your Cart is Empty

Back To Shop

የሚፈልጉትን ይዘዙን

Order what you want