በአዲስ አበባ መሥሪያ ቤቶች ተመሳሳይ ብሔር ያላቸው አመራሮች ብዛት ከ40 በመቶ እንዳይበልጥ ሊደረግ ነው Leave a comment

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአንድ የመንግሥት መሥሪያ ቤት ውስጥ ከሚኖሩ ዳይሬክተሮች እና ቡድን መሪዎች መካከል ተመሳሳይ የብሔር ማንነት ያላቸው አመራሮች ብዛት 40 በመቶ እንዳይበልጥ ሊያደርግ ነው።

የከተማ አስተዳደሩ በቅርቡ ለሚተገብረው የሠራተኞች ድልድል ሲባል 14 ሺህ በላይ የከተማ አስተደደሩ ሠራተኞች ነገ አርብ ታኅሣሥ 12/2016 .. ለፈተና እንደሚቀመጡ የአዲስ አበባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ለቢቢሲ ገልጿል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፤ ከማዕከል እስከ ወረዳ ድረስ ያሉት ተቋማትን አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል ባለፉት ሳምንታት ከሠራተኞቹ ጋር ውይይት ሲያደርግ ቆይቷል።

163 ሺህ ገደማ ሠራተኞች በስሩ ያሉት የከተማ አስተዳደሩ፤ በሚተገበረው ለውጥ ውስጥ ከተካተቱ ጉዳዮች መካከል የከተማዋን የመንግሥት ሠራተኞችን በአዲስ መልኩ መደልደል የሚለው ይገኝበታል።

ቢቢሲ የተመለከተው ለለውጡ ትግበራ የተዘጋጀ የሥልጠና ሰነድ እንደሚያመለክተው በመጀመሪያው ዙር ይህ ድልድል እንዲተገበርባቸው የተመረጡት የከተማ አስተዳደሩ 16 ተቋማት ናቸው።

ከእነዚህም መካከል የአዲስ አበባ ከተማ መሬት ልማት እና አስተዳደር፣ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር፣ ትራንስፖርት፣ ፐብሊክ ሰርቨሲ እና ሰው ሀብት ልማት፣ ፕላን እና ልማት፣ ሥራ እና ክህሎት፣ እንዲሁም ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮዎች ይገኙበታል።

ቤቶች ኮርፖሬሽን፣ ኅብረት ሥራ ኮሚሽን እንዲሁም ሌሎች የከተማይቱ ኤጀንሲዎች እና ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቶች በመጀመሪያው ዙር ድልድሉ ከሚተገበርባቸው መሥሪያ ቤቶች ውስጥ ተካትተዋል።

እነዚህ መሥሪያ ቤቶች ድልድል የሚደረግባቸው በማዕከል ቢሮዎቻቸው ብቻ ሳይሆን ክፍለ ከተማ እና ወረዳ ላይ ባሉ ጽህፈት ቤቶቻቸው ጭምር ነው።

እነዚህ መሥሪያ ቤቶች ለመጀመሪያው ዙር ትግበራ የተመረጡትብዙ ተገልጋይ የሚያስተናግዱ እንዲሁም ብልሹ አሰራር እና የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ብዙ መጓደል ያለባቸውበመሆናቸው እንደሆነ የፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊው / ጣሰው ገብሬ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

በአዲስ አበባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ የተዘጋጀው ሰነድ እንደሚያስረዳው አዲሱ የሠራተኞች ድልድል ከመከናወኑ በፊት የእነዚህ መሥሪያ ቤቶች ሠራተኞች ለፈተና ይቀመጣሉ።

የቢሮ ኃላፊው፤ የከተማ አስተዳደሩ ይህንን ፈተና ለመስጠት ያቀደው የሠራተኞቹንየብቃት ደረጃ ለማረጋገጥእንደሆነ ገልጸዋል።

ፈተናው የባህሪ እና የቴክኒክ ምዘናዎች እንደያዘ የገለጹት / ጣሰው፤የሚሰጠው የቴክኒክ ምዘና [ሠራተኞቹ] ከሚሠሩት ሥራ ጋር ግንኙነት ያለው ነው። የባህሪው [ፈተና] ደግሞ አገልግሎት አሰጣጡን የሚፈታተኑ የባህሪ ችግሮች ስላሉ ያንን ክፍተት ለመሙላት አመላካች እንዲሆን ተስቦ የተዘጋጀ ነውሲሉ የፈተናውን ይዘት አብራርተዋል።

ኃላፊው፤ ምዘናው በአዲስ አበባ እና ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲዎች በጋራ መዘጋጀቱን የገለጹ ሲሆን፣ ፈተናው የሚሰጠውም በዩኒቨርስቲ ወይም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ እንደሆነ ተናግረዋል። እስካሁን ባለው መረጃም ነገ አርብ ታኅሣሥ 12/2016 .. ፈተናውን የሚወስዱ ሠራተኞች ቁጥር 14 ሺህ በላይ እንደሆነ ጠቅሰዋል።

“[ፈተናውን] የማያልፉ [ሠራተኞች] እንዳይኖሩ ዝግጅት እንዲያደርጉ፣ እንዲያጠኑ ተነግሯል። ፈተናው ለማለፍ በሚያስቸግር መንገድ በጣም የተወሳሰበ፣ አብስትራክት እና ንድፈ ሀሳባዊ የሆነ ሳይሆን [የሠራተኞችን አቅም ለመለካት] አመላካች ሆኖ ነው የተዘጋጀው። ብዙዎቹ ሊያልፉ ይችላል የሚል ግምት ነው የተያዘውሲሉም የሚጠበቀውን ውጤት ገልጸዋል።

ቢቢሲ የተመለከተው የሪፎርም ሥልጠና ሰነድ እንደሚያስረዳው የከተማ አስተዳደሩ ባለሙያዎች ፈተናውን ለማለፍ 50 በመቶ በላይ ማምጣት ይጠበቅባቸዋል።ከዚህ [የማለፊያ ውጤት] በታች [የሆነ] ነጥብ ያገኘ ባለሙያ ከደረጃው ዝቅ ብሎ ባሉት የአስተዳደር እርከኖችላይ እንደሚመደብ ሰነዱ ላይ ሰፍሯል።

ለዳይሬክተሮች እና ለቡድን መሪዎች የተቀመጠው የፈተና ማለፊያ ነጥብ ደግሞ 60 በመቶ ሲሆን፤ ይህንን ነጥብ የማያስመዘግቡ አመራሮች ለዳይሬክተርነት ወይም ለቡድን መሪነት ኃላፊነት መወዳደር እንደማይችሉ ሰነዱ አስቀምጧል።

የከተማዋ የፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊው / ጣሰው፤ “[ሠራተኞች ፈተናውን] የማያልፉ ከሆነ ዝቅ ተደርገውም ሊመደቡ ይችላሉ። ድልድሉ ካለቀ በኋላ ሌሎች አማራጮችም ታይተው ምን ሊደረግ እንደሚችል የተለያዩ ዘዴዎችን ተጠቅሞ መፍትሄ ይፈለግላቸዋልሲሉ ተመሳሳይ ሀሳብ አንስተዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአዲስ መልኩ ሠራተኞቹን ሲደለድል ከፈተናም በተጨማሪ ሌሎች መስፈርቶችን እንደሚጠቀም / ጣሰው ገልጸዋል። የሥልጠና ሰነዱ የሠራተኞች ድልድልን በተመለከተትኩረት የሚሹ አዳዲስ ጉዳዮችበሚል ካስቀመጣቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ የብሔር ብሔረሰቦች ስብጥር ጉዳይ ነው።

ድልድሉ ሲከናወንሕብረ ብሔራዊነት እና አካታችነት በጥንቃቄመተግበር እንዳለበት በሰነዱ ላይ ሰፍሯል።አካታችነት እና ፍትሐዊነትንበሚመለከተው የሰነዱ ክፍል ላይ በዳይሬክተርነት እና ቡድን መሪነት የሥራ መደቦች ላይ አመራሮች ሲመደቡየሜሪት ሥርዓትእንደሚጠበቅ ያስረዳል።

ይሁንና ይህ የአመራሮች ድልድልየብሔር ብሔረሰብ ስብጥርን ባካተተ እና ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ባረጋገጠ መልኩእንደሚከናወን ይገልጻል። ሰነዱ አክሎም፤በመሥሪያ ቤቱ ካሉ የሥራ መደቦች [መካከል] በተመሳሳይ ማንነት የተያዙት 40 በመቶ መብለጥ የለባቸውምሲል ይህንን ድልድል በተመለከተ የአዲስ አበባ ከተማ ካቢኔ ባጸደቀው ደንብ ላይ የተቀመጠውን አሰራር ያስረዳል።

መሥሪያ ቤቶቹ ድልድሉን ሲያከናውኑ ይህንንን የብሔር ስብጥሩን ለመጠበቅ እንዲችሉብቃት ያላቸውን ሠራተኞች ከሌሎች መሥሪያ ቤቶች በመለየት በዝውውር እንዲሟሉእንደሚደረግም በሰነዱ ላይ ሰፍሯል።

የፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊው / ጣሰው ግን40 በመቶ መብለጥ የለበትምበሚል የተቀመጠው አሠራር፤ የሚተገበረው የቡድን መሪዎች እና ዳይሬክተሮች ድልድል ላይ ብቻ እንደሚሆን ለቢቢሲ ተናግረዋል።

በዚህ ድልድል ወደ ሠራተኛ የወረደ እንደዚህ ዓይነት ነገር የለም። የድልድል ደንቡ ውስጥም የለም። የተመሳሳይ ማንነት ያላቸው ከተወሰነ ፐርሰንት በላይ መሆን የለበትም የሚለው ለዳይሬክተሮች እና ለቡድን መሪዎች ነውሲሉ አብራርተዋል።

/ ጣሰው፤ከተማዋ የአገሪቱ ዋና ከተማ ናት። ብዙ ብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ያሉባት ስለሆነች ያንን ሥዕል የሚያሳይ እንዲሆን መደረግ ስላለበት የተቀመጠ ነገር ነውሲሉም ይህ አሠራር ተግባራዊ የሚደረግበትን ምክንያት ገልጸዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሚተገብረው ይህ የአገልግሎት አሰጣጥ ሪፎርም እና የሠራተኞች ድልድል እስከ ታኅሣሥ 25/2016 .. ድረስ ለማጠናቀቅ በጊዜያዊነት ዕቅድ መያዙን የፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊው / ጣሰው ተናግረዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በማዕከል መሥሪያ ቤቶች ያሉ ሠራተኞችን ወደ ወረዳዎች ለማሰራጨት ውሳኔ ያሳለፈው ባለፈው ኅዳር ወር ነው።

ካቢኔው በወቅቱ፤በማዕከል ደረጃ የሚታየውን የሠራተኛ ክምችት ከተማዋ ከምታመነጨው ገቢ እና ለሕብረተሰብ ከሚሰጠው አገልግሎት አንፃር የማይመጣጠን [ነው]” ሲል በወቅቱ ለውሳኔው መነሻ የሆነው ምክንያት ገልጾ ነበር። የከተማ አስተዳደሩ ሠራተኞችከፍተኛ የሥራ ጫና ወዳለባቸው ወረዳ እና ተቋማትየሚበተኑትሙያዊ እና ተፈላጊ ችሎታቸውንታሳቢ በማድረግ እንደሆነም የከተማዋ የከንቲባ ጽህፈት ቤት አስታውቆ ነበር።

 በድህረ ገጻችን ኢትዮ አማዞን በመግባት የሚፈልጉትን እቃ ማዝዝ  ብቻ  ሳይሆን የርስዎንም እቃዎች መሸጥ እንደሚችሉ ስናሳውቅዎት በደስታ ነው ለማስታወቂያ ወይንም ለመግቢያ ምንም ክፍያ አይጠበቅብዎትም፤  ለተጨማሪ መረጃ   ድህረ ገጻችንን ይጎብኙ።  https://ethio-amazon.com/

ለበለጠ መረጃ ሊንኩን በመንካት የቴሌግራም ግሩፓችንን ይቀላቀሉ!https://t.me/ethioamazonnnn

 

ምንጭ(ቢቢሲ)

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Cart

Your Cart is Empty

Back To Shop

የሚፈልጉትን ይዘዙን

Order what you want