” 2.5 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ሆኗል ” – የብሔራዊ ባንክ ገዥ……. Leave a comment

የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምሕረቱ ፥ እስካሁን ባለው ከዓለም አቀፉ የገንዘብ  ተቋም (IMF) እና ዓለም ባንክ 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ወደ ብሔራዊ ባንክ ገቢ መደረጉን ተናግረዋል።

በሌላ በኩል ፥ ከውጭ ከሚገቡ የፍጆታ ዕቃዎች 18 በመቶ ብቻ በውጭ ምንዛሬ እንደሚመጡ ገልፀዋል።

ሌሎቹ በአብዛኛው በኢ-መደበኛ ወይም በትይዩ ገበያ ወደ ሀገር ቤት ሲገቡ እንደነበር ጠቁመዋል።

በዚህም ” የምንዛሬ ተመኑ ወደ ገበያ መር መለወጡ በሸቀጦች ዋጋ ላይ ጭማሪ ሊፈጥር አይገባም ” ሲሉ ገልጸዋል።

ባንኩ ህገ-ወጥነትና አሉታዊ ጫና የሚፈጥሩ ጉዳዮች ከተከሰቱ ህጋዊ ምላሽ ለመስጠት መዘጋጀቱን ተናግረዋል።

በሌላ በኩል ፤ በፋይናንስ ተቋማት ላይ የሚከሰትን ህገወጥ አሰራር ለመቆጣጠር ጥብቅ የፊሲካል እና የገንዘብ ፖሊሲ ገቢራዊ ይደረጋል ሲሉ አውጀዋል።

በዚህም ” ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ በቂ ዝግጅት አድርገናል ” ብለዋል።

በድህረ ገጻችን ኢትዮ አማዞን በመግባት የሚፈልጉትን እቃ ማዘዝ  ብቻ  ሳይሆን የርስዎንም እቃዎች መሸጥ እንደሚችሉ ስናሳውቅዎት በደስታ ነው ። ለማስታወቂያ ወይንም ለመግቢያ ምንም ክፍያ አይጠበቅብዎትም፤  ለተጨማሪ መረጃ   ድህረ ገጻችንን ይጎብ/ኙ። https://ethio-amazon.com/

ለበለጠ መረጃ ሊንኩን በመንካት የቴሌግራም ግሩፓችንን ይቀላቀሉ!https://t.me/ethioamazon

ምንጭ፡– (@tikvahethiopia)

 

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Cart

Your Cart is Empty

Back To Shop