” ለኤጀንሲዎች ፈቃድ መስጠትም ሆነ መቆጣጠር የሚመለከተው እኛ ነው ” – የስራና ክህሎት ሚኒስቴር …. Leave a comment

ዜጎችን ለስራም ሆነ ለትምህርት ወደ ውጭ ሀገር የመላክ ፍቃድ ለስራና ክህሎት ሚኒስቴር ብቻ የተሰጠ ሃላፊነት መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል።

በዚህ ጉዳይ በሚኒስቴሩ የውጭ ሀገር ስራ ስምሪት የኤጀንሲዎች ፈቃድ መስጫ ዴስክ ሃላፊ አቶ ተክሌ ተስፉ ለመናኸሪያ ሬዲዮ 99.1 ቃላቸውን ሰጥተው ነበር።

” አሁን ላይ በተለያዩ ከተሞች በተለይ በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ ኤጀንሲዎች ሰዎችን ‘ ካናዳ እና ወደ ሌሎችም የውጭ ሀገራት ስራ እናስቀጥራችኃለን ‘ በሚል የሚያስተላለፉት ማስታወቂያ ፈጽሞ ፈቃድ የሌለው እና ህገ ወጥ ነው ‘ ብለዋል።

ይህን ስራ በሚሰሩት ላይ በጥቆማና በፍለጋ ሲደረስባቸው እርምጃ እንደሚወሰድባቸው ገልጸዋል።

” ለኤጀንሲዎች ፈቃድ መስጠቱንም ሆነ መቆጣጠሩንም የሚመለከተው የመንግስት ተቋም ስራና ክህሎት ሚኒስቴር ነው ” ሲሉ ገልጸዋል።

በፌደራልም በክልልም ያሉ ኤጀንሲዎች በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ፈቃድ ከተሰጣቸው ብቻ ስራው ላይ መሰማራት እንደሚችሉ አስገንዝበዋል።

በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች እየተበራከቱ መጥተዋል ያሏቸው ህገ ወጥ ኤጀንሲዎችን በጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር እርምጃ እንደሚወሰድባቸው አስጠንቅቀዋል።

ዜጎችን ያለ ፍቃድ ” ወደ ውጭ እንልካለን ” የሚሉ ህገ ወጦች ምንም አይነት እውቅና የሌላቸው መሆኑን ህብረተሰቡ እንዲረዳው ሲሉ ለሬድዮ ጣቢያው (መናኸሪያ 99.1 ኤፍ ኤም) በሰጡት ቃል አስገንዝበዋል።

በድህረ ገጻችን ኢትዮ አማዞን በመግባት የሚፈልጉትን እቃ ማዘዝ  ብቻ  ሳይሆን የርስዎንም እቃዎች መሸጥ እንደሚችሉ ስናሳውቅዎት በደስታ ነው ። ለማስታወቂያ ወይንም ለመግቢያ ምንም ክፍያ አይጠበቅብዎትም፤  ለተጨማሪ መረጃ   ድህረ ገጻችንን ይጎብኙ። https://ethio-amazon.com/

ለበለጠ መረጃ ሊንኩን በመንካት የቴሌግራም ግሩፓችንን ይቀላቀሉ!https://t.me/ethioamazon

ምንጭ ፡-(@tikvahethiopia)

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Cart

Your Cart is Empty

Back To Shop

የሚፈልጉትን ይዘዙን

Order what you want